ተቋሙ በመላ ኢትዮጵያ ሁሉን አቀፍ የእስልምና ትምህርት ፕሮግራሞችን እና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ይሰጣል።
ኢሙዳት ማህበረሰቡን በንጽጽር እውቀት በማሰልጠን ሌሎችን ወደኢስላም እንዲጠሩና የኢስላም አምባሳደር እንዲሆኑ ይሰራል።
ተልእኳችን በእውቀት፣ በእምነት (ኢማን) እና ማህበረሰብን በማገልገል ላይ የተመሰረተ ማዕከል መሆን ነው።
ከ2007 ዓ.ል ጀምሮ ኢሙዳት ከ10 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ ሙስሊሙን ማህበረሰብ ሲያገለግል ከትንሽ ድርጅትነት ወደ ትልቅ ተቋምነት በማደግ በአገር አቀፍ ደረጃ ተጽኖ አሳድሯል።
ሰፊ የንጽጽርና ኢስላማዊ ትምህርት ፕሮግራሞችን፣ የማህበረሰብ አገልግሎቶችን እና የመንፈሳዊ ልማት እድሎችን እናቀርባለን።
الفجر
الشروق
الظهر
العصر
المغرب
العشاء
የሰላት ሰዓት ሒሳብ የተደረገበት መንገድ:

ኢሙዳት መቀመጫውን አዲስ አበባ ያደረገ እና በመላው ኢትዮጵያ የሚገኙ ሙስሊም ማህበረሰቦችን ከፍ ለማድረግ የሚተጋ ብሄራዊ ለትርፍ ያልተቋቋመ ኢስላማዊ ድርጅት ነው። በአላህ እገዛ እና ችሮታ በትምህርት፣ በመስጊድ ግንባታ፣ በዳዕዋ (ኢስላማዊ ስርጭት) እና በሰብአዊ አገልግሎቶች ላይ በሰፊው እንሳተፋለን። ተልእኳችን በተለይም ሙስሊሞች አናሳ በሆኑባቸው የገጠር አካባቢዎች ብቁ፣ ጠንካራ፣ በኢማን ላይ የተመሰረቱ፣ በእውቀት የታጠቁ እና ጠንካራ ማህበራዊ አቅም ያላቸው ሙስሊም ማህበረሰቦችን መፍጠር ነው።
"በመላው ኢትዮጵያ በትክክለኛ እስላማዊ መርሆች ላይ ጸንቶ ከክህደት ስጋት የተጠበቀ እና በእውቀት፣ በእምነት እና በርህራሄ የሚያብብ፣ በመንፈሳዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ጠንካራ የሙስሊም ማህበረሰብ መገንባት ነው። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም (በተለይም በገጠር አካባቢ ያሉ ሙስሊም ማህበረሰቦች) ለኢስላማዊ ትምህርት፣ የማህበረሰብ ድጋፍ እና በቁርዓን እና በሱና ለሚመራ ዓላማ እድሉን ለመፍጠር እናልማለን።"
كُنتُمْ خَيْرَ أُمَّةٍ أُخْرِجَتْ لِلنَّاسِ تَأْمُرُونَ بِلْمَعْرُوفِ وَتَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنكَرِ وَتُؤْمِنُونَ بِللَّهِ ۗ وَلَوْ ءَامَنَ أَهْلُ الْكِتَـٰبِ لَكَانَ خَيْرًۭا لَّهُم ۚ مِّنْهُمُ الْمُؤْمِنُونَ وَأَكْثَرُهُمُ الْفَـٰسِقُونَ
“እናንተ ከሰው ሁሉ የተሻለ ሕዝብ ናችሁ፤ በበጎ ነገር ታዛላችሁ፣ ከክፉም ትከለክላላችሁ።”
ኣሊ-ዒምራን 3፡110
በእውቀት፣ በእምነት (ኢማን) እና በማህበረሰብ አገልግሎት የልህቀት ማዕከል ሆኖ ማገልገል
ኢስላማዊ እምነትን እና እሴቶችን በማጠናከር ማህበረሰቦችን ከክህደት እና ከአክፍሮት ኃይላት ግፊቶች መጠበቅ።
የእስልምናን መልእክት በጥበብ እና ሁሉን አቀፍ በሆነ የዳዕዋ ጥረት ለሌሎች ማካፈል።
አዲስ ለሰለሙ ወገኖች የትምህርት፣ ምክር እና የቁሳቁስ እርዳታ ማድረግ እና በመንፈሳዊ ጉዟቸው መደገፍ።
መስጊዶችን፣ መድረሳዎችን እና ሙስሊሙን ማህበረሰብ የሚያገለግሉ እና የሚያንጹ ተቋማትን መገንባት።
ጠንካራ የሙስሊም መሪዎችን ለማፍራት ለወጣቶች የአመራርንነት እና ኃይማኖታዊ ስልጠናዎችን መስጠት።
"አላማችን በአላህ ፍቃድ የኢትዮጵያን ሙስሊም ማህበረሰብ በመንፈሳዊ መነቃቃት እና በተግባራዊ አገልግሎት ከፍ ማድረግ ነው።"
ኢሙዳት በኢትዮጵያ የሚገኘውን ሙስሊም ማህበረሰብ ለመደገፍ እና ኢስላማዊ እሴቶችን በትምህርት እና በማስተዋወቅ የተለያዩ አገልግሎቶችን ይሰጣል።
ሙስሊሞች ጥቂት በሆኑባቸው አካባቢዎች ላሉ ሙስሊሞች የተዋቀረ ኢስላማዊ እውቀትን ለማዳረስ የተለያዩ ኮርሶችን እና የትምህርት ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት እና መስጠት
የአምልኮ፣ የመማሪያ እና የማህበረሰብ ድጋፍ ማእከል ሆነው እንዲያገለግሉ በማሰብ የመስጊዶችን እና መድረሳዎችን ግንባታ እና እድሳት መርዳት
በድህነት ምክንያት ለሚሲዮናዊ ጫና ተጋላጭ ለሆኑ ሙስሊሞች የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ክብራቸው እና እምነታቸው መጠበቁን ማረጋገጥ
ሙስሊሞች ስለተለያዩ እምነት እውቀት እንዲኖራቸው እና ውጤታማ የዳዕዋ እንቅስቃሴ ላይ ይሳተፉ ዘንድ የተለያዩ ኮርሶችን መስጠት
በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች እና ወጣቶች ኢስላማዊ ማንነታቸውን እና ጽናታቸውን እንዲያጠናክሩ እና በዕውቀት የሚመሩ፣ ንቁ የማህበረሰብ መሪዎች እንዲሆኑ የሚያግዙ ፕሮግራሞችን ማዘጋጀት
እስልምናን በጥበብ እና ግልጽ በሆነ መንገድ ለማስፋፋት የዳዕዋ ዘመቻዎችን፣ ህዝባዊ መድረኮችን እና ውይይቶችን በማዘጋጀት
በሃገር ውስጥ ቋንቋዎች ትክክለኛ ኢስላማዊ መጽሃፎችን፣ ፓምፍሌቶችን እና የመልቲሚዲያ ቁሳቁሶችን ማምረት እና ማከፋፈል
ዳኢዎች ማህበረሰባቸው በብቃት ለማገልገል፣ ለመምራት እና ለማስተማር የሚያስፈልጓቸውን ልምዶች ያዳብሩ ዘንድ ስልጠናዎችን ማዘጋጀት

ወጣቶች ሴኩላሪዝምን እና የሚሲዮናዊያንን ተፅእኖ እንዲቋቋሙ እና እምነታቸውን እና ማህበረሰባቸውን እንዲጠብቁ ማስታጠቅ

ወቅታዊ እስላማዊ የወጣቶች ስልጠና (አዲስ አበባ)

ኢስላማዊ ማዕከላት

የቁርዓን ስርጭት

የኢስላማዊ መጽሐፍት እና ፓምፍሌቶች ስርጭት

የመስጂድ ግንባታ

የመድረሳ ግንባታ

የኡስታዞችና ተማሪዎች ድጋፍ ፕሮግራም

ለአዳዲስ ሰለምቴዎች የትምህርት ፕሮግራም

ኢስላማዊ መርከዞች

ለኡስታዞች የሞተርሳይክል ድጋፍ

የሚሞሪ ካርድ ስርጭት

የውሃ ጉድጓድ ግንባታ

ፍየል ፕሮጀክት

አመታዊ የአንድ ወር የኢፍጣር ፕሮግራም
ላለፉት አስርት አመታት በለጋስ ደጋፊዎቻችን እርዳታ አማካኝነት አስደናቂ ክንዋኔዎችን አስመዝግበናል።
የአምልኮ እና የማህበረሰብ ህይወት ማዕከሎች ሆነው የሚያገለግሉ መስጂዶች ተሰርተዋል
"ለአላህ ብሎ መስጂድ የገነባ አላህ በጀነት ውስጥ ቤት ይገነባለታል።"
ቁርአን፣ አረብኛ እና ዓለማዊ ትምህርቶችን በመድረሳዎቻችንና ትምህርት ቤቶቻን እየተማሩ ይገኛሉ።
በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ላሉ ቤተሰቦች ቁርኣንን በተለያዩ ቋንቋዎች አቅርበናል።
ሰለምቴዎችን በመሰረታዊ ኢስላማዊ ትምህርቶች እና ማህበራዊ አገልግሎቶች እገዛ አቅርበናል።
ለተቸገሩ ቤተሰቦች የረመዳን ኢፍጣሮች፣ የምግብ ቅርጫቶች እና አስፈላጊ ቁሳቁሶችን አቅርበናል።
ለወላጅ አልባ ህጻናትን እና መበለቶች ቀጥተኛ የገንዘብ ድጋፍ፣ የጤና አገልግሎት እና እንክብካቤ አቅርበናል።
የእርስዎ ለጋስ ልገሳ ኢስላማዊ እሴቶችንና እውቀቶች ለማህበረሰባችን የማስተዋወቅና የማስተማር ተልእኳችንን እንድንቀጥል ይረዳናል።
ለህፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአዋቂዎች የሚሰጡ ኢስላማዊ ትምህርትን ይደግፋል።
በመላው ኢትዮጵያ መስጂዶችን ለመገንባት እና ለመንከባከብ እገዛ ያደርጋል።
በረመዷን ለተቸገሩ ቤተሰቦች የኢፍጣር ምግብ ለማቅረብ ይውላል።
የውሃ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች የገንዘብ ጉድጓዶች ለማስቆፈር ይውላል።
ሙስሊሞች አናሳ በሆኑባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ ኢማሞች፣ ኡስታዞች እና ሙስሊሞች የህክምና አገልግሎት ይደግፋል።
ችግር ያለባቸውን ቤተሰቦች በምግብ እና በአቅርቦት ለመርዳት ይውላል።
ወደ ንግድ ባንክ ሒሳባችን በቀጥታ ለማስተላለፍ።
Account Name
ETHIOPIAN ISLAMIC ASSOCIATION FOR DAE'WA AND EDUCATION
Account Number
1000606391448